Loading surah...
Back to Amharic Quran
60 Ayahs • Meccan
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ وَٱلذَّٰرِيَٰتِ ذَرْوًۭا
መበተንን በታኞች በኾኑት (ነፋሶች)፡፡
فَٱلْحَٰمِلَٰتِ وِقْرًۭا
ከባድ (ዝናምን) ተሸካሚዎች በኾኑትም (ደመናዎች)፡፡
فَٱلْجَٰرِيَٰتِ يُسْرًۭا
ገር (መንሻለልን) ተንሻላዮች በኾኑትም (መርከቦች)፡፡
فَٱلْمُقَسِّمَٰتِ أَمْرًا
ነገርን ሁሉ አከፋፋዮች በኾኑትም (መላእክት) እምላለሁ፡፡
إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَصَادِقٌۭ
የምትቀጠሩት (ትንሣኤ) እውነት ነው፡፡
وَإِنَّ ٱلدِّينَ لَوَٰقِعٌۭ
(እንደየሥራው) ዋጋን ማግኘትም፤ ኋኝ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡
وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلْحُبُكِ
የ(ከዋክብት) መንገዶች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
إِنَّكُمْ لَفِى قَوْلٍۢ مُّخْتَلِفٍۢ
እናንተ (የመካ ሰዎች) በተለያየ ቃል ውስጥ ናችሁ፡፡
يُؤْفَكُ عَنْهُ مَنْ أُفِكَ
ከርሱ የሚዝዞር ሰው ይዝዞራል፡፡
قُتِلَ ٱلْخَرَّٰصُونَ
በግምት የሚናገሩ ውሸታሞች ተረገሙ፡፡
ٱلَّذِينَ هُمْ فِى غَمْرَةٍۢ سَاهُونَ
እነዚያ እነርሱ በሚሸፍን ስሕተተ ውስጥ ዘንጊዎች የኾኑት፡፡
يَسْـَٔلُونَ أَيَّانَ يَوْمُ ٱلدِّينِ
የዋጋ መስጫው ቀን መቼ እንደ ኾነ ይጠይቃሉ፡፡
يَوْمَ هُمْ عَلَى ٱلنَّارِ يُفْتَنُونَ
(እነርሱ) በእሳት ላይ በሚፈተኑበት ቀን ነው፡፡
ذُوقُوا۟ فِتْنَتَكُمْ هَٰذَا ٱلَّذِى كُنتُم بِهِۦ تَسْتَعْجِلُونَ
«መከራችሁን ቅመሱ፤ ይህ ያ በእርሱ ትቻኮሉበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡
إِنَّ ٱلْمُتَّقِينَ فِى جَنَّٰتٍۢ وَعُيُونٍ
አላህን ፈሪዎቹ በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
ءَاخِذِينَ مَآ ءَاتَىٰهُمْ رَبُّهُمْ ۚ إِنَّهُمْ كَانُوا۟ قَبْلَ ذَٰلِكَ مُحْسِنِينَ
ያንን ጌታቸው የሰጣቸውን ተቀባዮች ኾነው፤ (በገነት ውስጥ ይኾናሉ)፡፡ እነርሱ ከዚህ በፊት መልካም ሰሪዎች ነበሩና፡፡
كَانُوا۟ قَلِيلًۭا مِّنَ ٱلَّيْلِ مَا يَهْجَعُونَ
ከሌሊቱ ጥቂትን ብቻ ይተኙ ነበሩ፡፡
وَبِٱلْأَسْحَارِ هُمْ يَسْتَغْفِرُونَ
በሌሊቱ መጨረሻዎችም እነርሱ ምሕረትን ይለምናሉ፡፡
وَفِىٓ أَمْوَٰلِهِمْ حَقٌّۭ لِّلسَّآئِلِ وَٱلْمَحْرُومِ
በገንዘቦቻቸውም ውስጥ ለለማኝና (ከልመና) ለተከለከለም (በችሮታቸው) መብት አልለ፡፡
وَفِى ٱلْأَرْضِ ءَايَٰتٌۭ لِّلْمُوقِنِينَ
በምድርም ውስጥ ለሚያረጋግጡ ሰዎች ምልክቶች አልሉ፡፡
Page 1 of 3 (60 ayahs)