Loading surah...
Back to Amharic Quran
62 Ayahs • Meccan
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ وَٱلنَّجْمِ إِذَا هَوَىٰ
በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡
مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمْ وَمَا غَوَىٰ
ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡
وَمَا يَنطِقُ عَنِ ٱلْهَوَىٰٓ
ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡
إِنْ هُوَ إِلَّا وَحْىٌۭ يُوحَىٰ
እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
عَلَّمَهُۥ شَدِيدُ ٱلْقُوَىٰ
ኀይሎቹ ብርቱው (መልአክ) አስተማረው፡፡
ذُو مِرَّةٍۢ فَٱسْتَوَىٰ
የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡
وَهُوَ بِٱلْأُفُقِ ٱلْأَعْلَىٰ
እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡
ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ
ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡
فَكَانَ قَابَ قَوْسَيْنِ أَوْ أَدْنَىٰ
(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡
فَأَوْحَىٰٓ إِلَىٰ عَبْدِهِۦ مَآ أَوْحَىٰ
ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡
مَا كَذَبَ ٱلْفُؤَادُ مَا رَأَىٰٓ
(ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡
أَفَتُمَٰرُونَهُۥ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ
ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?
وَلَقَدْ رَءَاهُ نَزْلَةً أُخْرَىٰ
በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡
عِندَ سِدْرَةِ ٱلْمُنتَهَىٰ
በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤
عِندَهَا جَنَّةُ ٱلْمَأْوَىٰٓ
እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡
إِذْ يَغْشَى ٱلسِّدْرَةَ مَا يَغْشَىٰ
ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡
مَا زَاغَ ٱلْبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ
ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡
لَقَدْ رَأَىٰ مِنْ ءَايَٰتِ رَبِّهِ ٱلْكُبْرَىٰٓ
ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡
أَفَرَءَيْتُمُ ٱللَّٰتَ وَٱلْعُزَّىٰ
አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?
وَمَنَوٰةَ ٱلثَّالِثَةَ ٱلْأُخْرَىٰٓ
ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?)
Page 1 of 4 (62 ayahs)