Loading surah...
Back to Amharic Quran
52 Ayahs • Meccan
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ نٓ ۚ وَٱلْقَلَمِ وَمَا يَسْطُرُونَ
ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡
مَآ أَنتَ بِنِعْمَةِ رَبِّكَ بِمَجْنُونٍۢ
አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡
وَإِنَّ لَكَ لَأَجْرًا غَيْرَ مَمْنُونٍۢ
ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡
وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَظِيمٍۢ
አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡
فَسَتُبْصِرُ وَيُبْصِرُونَ
ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡
بِأَييِّكُمُ ٱلْمَفْتُونُ
ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡
إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعْلَمُ بِٱلْمُهْتَدِينَ
ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡
فَلَا تُطِعِ ٱلْمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡
وَدُّوا۟ لَوْ تُدْهِنُ فَيُدْهِنُونَ
ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡
وَلَا تُطِعْ كُلَّ حَلَّافٍۢ مَّهِينٍ
ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡
هَمَّازٍۢ مَّشَّآءٍۭ بِنَمِيمٍۢ
ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡
مَّنَّاعٍۢ لِّلْخَيْرِ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ
ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤
عُتُلٍّۭ بَعْدَ ذَٰلِكَ زَنِيمٍ
ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡
أَن كَانَ ذَا مَالٍۢ وَبَنِينَ
የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡
إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ ءَايَٰتُنَا قَالَ أَسَٰطِيرُ ٱلْأَوَّلِينَ
በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
سَنَسِمُهُۥ عَلَى ٱلْخُرْطُومِ
በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡
إِنَّا بَلَوْنَٰهُمْ كَمَا بَلَوْنَآ أَصْحَٰبَ ٱلْجَنَّةِ إِذْ أَقْسَمُوا۟ لَيَصْرِمُنَّهَا مُصْبِحِينَ
እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡
وَلَا يَسْتَثْنُونَ
(በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡
فَطَافَ عَلَيْهَا طَآئِفٌۭ مِّن رَّبِّكَ وَهُمْ نَآئِمُونَ
እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡
فَأَصْبَحَتْ كَٱلصَّرِيمِ
እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡
Page 1 of 3 (52 ayahs)