Loading surah...
Back to Amharic Quran
56 Ayahs • Meccan
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ يَٰٓأَيُّهَا ٱلْمُدَّثِّرُ
አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!
قُمْ فَأَنذِرْ
ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡
وَرَبَّكَ فَكَبِّرْ
ጌታህንም አክብር፡፡
وَثِيَابَكَ فَطَهِّرْ
ልብስህንም አጥራ፡፡
وَٱلرُّجْزَ فَٱهْجُرْ
ጣዖትንም ራቅ፡፡
وَلَا تَمْنُن تَسْتَكْثِرُ
ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ
وَلِرَبِّكَ فَٱصْبِرْ
ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡
فَإِذَا نُقِرَ فِى ٱلنَّاقُورِ
በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
فَذَٰلِكَ يَوْمَئِذٍۢ يَوْمٌ عَسِيرٌ
ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
عَلَى ٱلْكَٰفِرِينَ غَيْرُ يَسِيرٍۢ
በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡
ذَرْنِى وَمَنْ خَلَقْتُ وَحِيدًۭا
አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
وَجَعَلْتُ لَهُۥ مَالًۭا مَّمْدُودًۭا
ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
وَبَنِينَ شُهُودًۭا
(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
وَمَهَّدتُّ لَهُۥ تَمْهِيدًۭا
ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡
ثُمَّ يَطْمَعُ أَنْ أَزِيدَ
ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡
كَلَّآ ۖ إِنَّهُۥ كَانَ لِءَايَٰتِنَا عَنِيدًۭا
ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
سَأُرْهِقُهُۥ صَعُودًا
በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡
إِنَّهُۥ فَكَّرَ وَقَدَّرَ
እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
فَقُتِلَ كَيْفَ قَدَّرَ
ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!
ثُمَّ قُتِلَ كَيْفَ قَدَّرَ
ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!
Page 1 of 3 (56 ayahs)