Loading surah...
Back to Amharic Quran
25 Ayahs • Meccan
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنشَقَّتْ
ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤
وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ
ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤
وَإِذَا ٱلْأَرْضُ مُدَّتْ
ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤
وَأَلْقَتْ مَا فِيهَا وَتَخَلَّتْ
በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤
وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ
ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡
يَٰٓأَيُّهَا ٱلْإِنسَٰنُ إِنَّكَ كَادِحٌ إِلَىٰ رَبِّكَ كَدْحًۭا فَمُلَٰقِيهِ
አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡
فَأَمَّا مَنْ أُوتِىَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤
فَسَوْفَ يُحَاسَبُ حِسَابًۭا يَسِيرًۭا
በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡
وَيَنقَلِبُ إِلَىٰٓ أَهْلِهِۦ مَسْرُورًۭا
ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡
وَأَمَّا مَنْ أُوتِىَ كِتَٰبَهُۥ وَرَآءَ ظَهْرِهِۦ
መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤
فَسَوْفَ يَدْعُوا۟ ثُبُورًۭا
(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡
وَيَصْلَىٰ سَعِيرًا
የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡
إِنَّهُۥ كَانَ فِىٓ أَهْلِهِۦ مَسْرُورًا
እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡
إِنَّهُۥ ظَنَّ أَن لَّن يَحُورَ
እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡
بَلَىٰٓ إِنَّ رَبَّهُۥ كَانَ بِهِۦ بَصِيرًۭا
አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡
فَلَآ أُقْسِمُ بِٱلشَّفَقِ
አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡
وَٱلَّيْلِ وَمَا وَسَقَ
በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤
وَٱلْقَمَرِ إِذَا ٱتَّسَقَ
በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡
لَتَرْكَبُنَّ طَبَقًا عَن طَبَقٍۢ
ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡
فَمَا لَهُمْ لَا يُؤْمِنُونَ
የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?
Page 1 of 2 (25 ayahs)