Loading surah...
Back to Amharic Quran
30 Ayahs • Meccan
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ وَٱلْفَجْرِ
በጎህ እምላለሁ፡፡
وَلَيَالٍ عَشْرٍۢ
በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
وَٱلشَّفْعِ وَٱلْوَتْرِ
በጥንዱም በነጠላውም፡፡
وَٱلَّيْلِ إِذَا يَسْرِ
በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡
هَلْ فِى ذَٰلِكَ قَسَمٌۭ لِّذِى حِجْرٍ
በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?
أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِعَادٍ
ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?
إِرَمَ ذَاتِ ٱلْعِمَادِ
በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
ٱلَّتِى لَمْ يُخْلَقْ مِثْلُهَا فِى ٱلْبِلَٰدِ
በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
وَثَمُودَ ٱلَّذِينَ جَابُوا۟ ٱلصَّخْرَ بِٱلْوَادِ
በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
وَفِرْعَوْنَ ذِى ٱلْأَوْتَادِ
በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡
ٱلَّذِينَ طَغَوْا۟ فِى ٱلْبِلَٰدِ
በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡
فَأَكْثَرُوا۟ فِيهَا ٱلْفَسَادَ
በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)
فَصَبَّ عَلَيْهِمْ رَبُّكَ سَوْطَ عَذَابٍ
በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡
إِنَّ رَبَّكَ لَبِٱلْمِرْصَادِ
ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡
فَأَمَّا ٱلْإِنسَٰنُ إِذَا مَا ٱبْتَلَىٰهُ رَبُّهُۥ فَأَكْرَمَهُۥ وَنَعَّمَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّىٓ أَكْرَمَنِ
ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡
وَأَمَّآ إِذَا مَا ٱبْتَلَىٰهُ فَقَدَرَ عَلَيْهِ رِزْقَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّىٓ أَهَٰنَنِ
በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡
كَلَّا ۖ بَل لَّا تُكْرِمُونَ ٱلْيَتِيمَ
ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡
وَلَا تَحَٰٓضُّونَ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلْمِسْكِينِ
ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡
وَتَأْكُلُونَ ٱلتُّرَاثَ أَكْلًۭا لَّمًّۭا
የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡
وَتُحِبُّونَ ٱلْمَالَ حُبًّۭا جَمًّۭا
ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡
Page 1 of 2 (30 ayahs)