Loading...
Language: Amharic
አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንደተረኩት፡ የአላህ መልእክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- «ከእናንተ አንዳችሁ በሚተኛበት ጊዜ፣ ሰይጣን በጭንቅላቱ ጀርባ ላይ ሶስት ቋጠሮዎችን ያስራል። በእያንዳንዱ ቋጠሮ ላይ እነዚህን ቃላት እያነበበ ይተነፍሳል፡ “ሌሊቱ ረጅም ነው፣ ስለዚህ ተኛ።” አንድ ሰው ሲነቃ እና አላህን ሲያወሳ፣ አንድ ቋጠሮ ይፈታል፤ እና ውዱእ ሲያደርግ፣ ሁለተኛው ቋጠሮ ይፈታል፤ እና ሲሰግድ፣ ሶስተኛው ቋጠሮ ይፈታል እናም ጠዋት ላይ በንቃት እና በጥሩ ልብ ይነሳል፤ አለበለዚያ ሰነፍ እና በመጥፎ ልብ (ስሜት) ይነሳል።»
Reference: ቡኻሪ፡ ፲፩፻፵፪