Loading...
Language: Amharic
أَبْلَ وَأَخْلَقْ
አብላ ወ አኽላቅ
ልበስ እና ጨርስ (አሮጌ አድርገው)። (ማለትም አላህ እድሜህን ያረዝምልህ እና ልብሱ እስኪያልቅ ድረስ ልበሰው)። ኡሙ ኻሊድ (ረ.ዐ)፣ የኻሊድ ኢብን ሰይድ (ረ.ዐ) ልጅ እንዲህ አለች፡- «ጥቁር ንድፍ ያለው ልብስ ወደ የአላህ መልእክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ተመጣ። ከዚያ እርሳቸው አሉ፡- “ይህንን ልብስ ለማን ማልበስ እንችላለን?” ሶሃቦች ዝም ሲሉ፣ ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) አሉ፡- “ኡሙ ኻሊድን አምጡልኝ።” ከዚያ ወደ ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) በተመጣሁ ጊዜ፣ ልብሱን በገዛ እጃቸው አለበሱኝ። ከዚያም ሁለት ጊዜ እንዲህ አሉ- (ዱዓው ከላይ ተጠቅሷል)። ይህ የሆነው ኡሙ ኻሊድ ገና በጣም ወጣት እያለች ከአባቷ ጋር ከኢትዮጵያ ወደ መዲና በተሰደደች ጊዜ ነው።»
Reference: ቡኻሪ፡ ፶፱፻፺፫