Loading...
Language: Amharic
የሙአዚኑን ተሸሁድ (ማለትም አሽሀዱ አነ ሙሀመደር...) ከተናገሩ በኋላ አድማጮቹ ይህንን ዚክር ይላሉ -
أَشْهَدُ أَنْ لَا إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ وَأَنَّ مُحَمَّدًا عَبْدُهُ وَرَسُولُهُ رَضِيتُ بِاللَّهِ رَبًّا وَبِمُحَمَّدٍ رَسُولًا وَبِالْإِسْلَامِ دِينًا
አሽ-ሀዱ አን ላ ኢላሀ ኢለላሁ ወህደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ወ አነ ሙሀመደን አብዱሁ ወ ረሱሉሁ፣ ረዲቱ ቢላሂ ረበን ወ ቢሙሀመዲን ረሱለን ወ ቢል-ኢስላሚ ዲን-ን
ከአላህ በስተቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ፣ ብቻውን እንደሆነ፣ አጋር እንደሌለው እና ሙሐመድ አገልጋዩ እና መልእክተኛው (ሶ.ዐ.ወ) መሆናቸውን እመሰክራለሁ። በአላህ ጌታነት፣ እና በሙሐመድ መልእክተኛነት እና በኢስላም ሃይማኖትነት ወድጃለሁ። ሰዕድ ኢብን አቢ ወቃስ (ረ.ዐ) እንዳሉት፡ የአላህ መልእክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡ «ሙአዚኑን የሰማ እና እነዚህን ቃላት የተናገረ፣ ወንጀሎቹ ሁሉ ይማሩለታል።»
Reference: ሙስሊም፡ ፫፻፹፮