Loading...
Language: Amharic
سُبْحَانَكَ اَللَّهُمَّ وَبِحَمْدِكَ، أَشْهَدُ أَنْ لَا إِلَهَ إِلاَّ أَنْتَ، أَسْتَغْفِرُكَ وَأَتُوْبُ إِلَيْكَ
ሱብሀነከ አላሁመ ወ ቢሀምዲከ፣ አሽ-ሀዱ አን ላ ኢላሀ ኢላ አንተ፣ አስተግፊሩከ ወ አቱቡ ኢለይክ
ጥራት ይገባህ አላህ ሆይ፣ ምስጋናም ላንተ ነው፤ ከአንተ በስተቀር የሚመለክ አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ። ምህረትህን እጠይቃለሁ እና በንስሃ ወደ አንተ እመለሳለሁ። አቡ ሰይድ (ረ.ዐ) እንዳሉት፣ ረሱሉላህ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፣ አንድ ሰው ከውዱ በኋላ ይህንን ዱዓ ካለ፣ በደብዳቤ ተጽፎ ይታተማል (ከዙፋኑ በታች)። ያ ማህተም ከትንሳኤ በፊት አይሰበርም።
Reference: አን-ነሳኢ፣ አመለል-የውም ወል-ለይላ፣ ገጽ ፻፸፫። እንዲሁም አል-አልባኒ፣ ኢርዋኡል-ገሊል ፩/፻፴፭ እና ፪/፺፬ ይመልከቱ።