Loading...
Language: Amharic
ጃቢር ኢብን አብዲላህ (ረ.ዐ) እንደዘገቡት፡ በረጅሙ የነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ሐጅ ሀዲሳቸው ላይ በአንድ ወቅት እንዲህ አሉ፡ “ከዚያም የአላህ መልእክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እስኪነጋ ድረስ ተኙ። ጠዋቱ ግልፅ ከሆነ በኋላ፣ በአንድ አዛን እና በአንድ ኢቃማ የፈጅርን ሶላት ሰገዱ። ከዚያም በቀስዋ [1] ላይ ሆነው ወደ አል-መሽአሩል ሀራም መጡ። እዚያም ወደ ቂብላ ዞሩ እና ወደ አላህ ተማፀኑ እና የአላህን ታላቅነት፣ ሉዓላዊነት እና አንድነት አወጁ። የጠዋቱ ብርሃን በጣም እስኪደምቅ ድረስ እዚያ ቆዩ። ከዚያም ፀሐይ ከመውጣቷ በፊት ሄዱ።' [2]
Reference: [፩] የነቢዩ (ﷺ) መጓጓዣ ስም [፪] ሙስሊም፡ ፲፪፻፲፰