Loading...
Language: Amharic
1. ከሰይጣን በአላህ መጠበቅ፤ 2. አዛን ማድረግ [1] 3. ዚክር እና ቁርአን መቅራት፤ እና [2] 4. በሶላት እና በቁርአን ንባብ ወቅት ወደ ግራ ሶስት ጊዜ መትፋት። በተጨማሪም፣ ሰይጣናትን የሚያርቁ ሌሎች ነገሮች የጠዋት እና የማታ አዝካሮች፣ የእንቅልፍ አዝካሮች፣ የመንቃት አዝካሮች፣ ወደ ቤት የመግባት እና የመውጣት አዝካሮች፣ ወደ መስጊድ የመግባት እና የመውጣት አዝካሮች፣ ወዘተ፣ እና እነዚያ በሸሪዓ መሰረት የሆኑ አዝካሮች ናቸው። ለምሳሌ፣ አያቱል ኩርሲ፣ በእንቅልፍ ወቅት የሱረቱል በቀራህ የመጨረሻዎቹ ሁለት አንቀጾች። በተጨማሪም፣ “ላ ኢላሀ ኢለላሁ ወህደሁ ላ ሸሪከ ለሁ፣ ለሁል ሙልኩ ወ ለሁል ሀምዱ፣ ወሁወ አላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር” መቶ ጊዜ የሚቀራ ሰው፣ ለዚያ ቀን ሙሉ ጥበቃ ይሰጠዋል። እንዲሁም አዛን ሲሰጥ ሰይጣን ይሸሻል። ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) “ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ። በእርግጥ ሰይጣን ሱረቱል በቀራህ ከሚቀራበት ቤት ይሸሻል።” ብለዋል::
Reference: [፩] ቡኻሪ፡ ፮፻፰ [፪] ሙስሊም፡ ፯፻፹