Loading...
Language: Amharic
በአሊ ኢብን አቡ ጣሊብ እንደተዘገበው፡ አቡ በክር አንድ ሀዲስ ነገሩኝ፣ እና አቡ በክር በጉነት ነገረው። እሱም አለ፡ የአላህ መልእክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ፡- አንድ (የአላህ) ባርያ ኃጢአትን ሲሰራ፣ እና ውዱን በደንብ ሲያደርግ፣ እና ከዚያም ቆሞ ሁለት ረካዓዎችን ሲሰግድ፣ እና አላህን ምህረትን ሲጠይቅ፣ አላህ ምህረት ያደርግለታል። ከዚያም ይህንን አንቀጽ ቀሩ፡- እነዚያም መጥፎን በሰሩ ወይም ነፍሶቻቸውን በበደሉ ጊዜ አላህን የሚያስታውሱና ለኃጢአቶቻቸው ምህረትን የሚለምኑ፣ ከላህም ሌላ ኃጢአቶችን የሚምር ማን ነው? በእርሱም በሰሩት ላይ እነርሱ የሚያውቁ ሲሆኑ የማይዘወትሩ ናቸው። እነዚያ፣ ምንዳቸው ከጌታቸው የሆነ ምህረትና ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች ናቸው፣ በውስጧ ዘውታሪዎች ሲሆኑ፤ የሠራተኞችም ምንዳ ምን ያምር! (ሱረቱ ኣሊ-ዒምራን 3፡ 135-136)
Reference: ሰሂህ (አልባኒ)። አቡ ዳውድ፡ ፲፭፻፳፩