Loading...
Language: Amharic
አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንደተረኩት፡ የአላህ መልእክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ለመተኛት ስንሄድ እንዲህ እንድንል ያዙን ነበር፡
اَللَّهُمَّ رَبَّ السَّمَوَاتِ السَّبْعِ وَرَبَّ الْأَرْضِ، وَرَبَّ الْعَرْشِ الْعَظِيمِ، رَبَّنَا وَرَبَّ كُلِّ شَيْءٍ، فَالِقَ الْحَبِّ وَالنَّوَى، وَمُنْزِلَ التَّوْرَاةِ وَالْإِنْجِيلِ، وَالْفُرْقَانِ، أَعُوْذُ بِكَ مِنْ شَرِّ كُلِّ شَيْءٍ أَنْتَ آخِذٌ بِنَاصِيَتِهِ اَللَّهُمَّ أَنْتَ الْأَوَّلُ فَلَيْسَ قَبْلَكَ شَيْءٌ، وَأَنْتَ الْآخِرُ فَلَيسَ بَعْدَكَ شَيْءٌ، وَأَنْتَ الظَّاهِرُ فَلَيْسَ فَوْقَكَ شَيْءٌ، وَأَنْتَ الْبَاطِنُ فَلَيْسَ دُونَكَ شَيْءٌ، اِقْضِ عَنَّا الدَّيْنَ وَأَغْنِنَا مِنَ الْفَقْرِ
አላሁመ ረበስ-ሰማዋቲስ-ሰባ፣ ወ ረበል-አርዲ፣ ወ ረበል-አርሺል-አዚም፣ ረበና ወ ረበ ኩሊ ሸይኢን፣ ፋሊቀል-ሀቢ ወነዋ፣ ወ ሙንዚለተ-ተውራቲ ወል-ኢንጂሊ፣ ወል-ፉርቃን፣ አኡዙ ቢከ ሚን ሸሪ ኩሊ ሸይኢን አንተ አኺዙን ቢናሲየቲሂ። አላሁመ አንተል-አወሉ ፈለይሰ ቀብለከ ሸይኡን፣ ወ አንተል-አኺሩ ፈለይሰ በአደከ ሸይኡን፣ ወ አንተድ-ዳሂሩ ፈለይሰ ፈውቀከ ሸይኡን፣ ወ አንተል-ባጢኑ ፈለይሰ ዱነከ ሸይኡን፣ ኢቅዲ አንናድ-ደይነ ወ አግኒና ሚነል-ፈቅር
አላህ ሆይ፣ የሰባቱ ሰማያት ጌታ እና የታላቁ ዙፋን ጌታ፣ የኛ ጌታ እና የሁሉም ነገር ጌታ፣ የፍሬ እና የተምር እምብርት ሰንጣቂ፣ የተውራት፣ የኢንጂል እና የፉርቃን አውራጅ፣ አንተ ግንባሩን ከያዝከው ከሁሉም ነገር ክፋት በአንተ እጠበቃለሁ። አላህ ሆይ፣ አንተ የመጀመሪያው ነህ ከአንተ በፊት ምንም የለም፣ እና አንተ የመጨረሻው ነህ ከአንተ በኋላ ምንም የለም፣ አንተ ግልጽ ነህ ከአንተ በላይ ምንም የለም፣ እና አንተ ስውር ነህ ከአንተ ወዲያ (የሚቀርብ) ምንም የለም። ዕዳችንን ክፈልልን እና ከድህነት ጠብቀን።
Reference: ሙስሊም፡ ፪፯፩፫፣ ሷሒሕ። ቲርሚዚ፡ ፫፬፹፩