Loading...
Language: Amharic
አብዱላህ ኢብን መስዑድ (ረ.ዐ) እንደተረኩት፡ የአላህ መልእክተኛ (ሶ.ዐ.ወ)፣ አንድ ባሪያ ማንኛውም ጭንቀት ወይም ስጋት ካጋጠመው፣ ከዚያ እንዲህ ይበል አሉ፡
اَللَّهُمَّ إِنِّي عَبْدُكَ، وَابْنُ عَبْدِكَ، وَابْنُ أَمَتِكَ، نَاصِيَتِي بِيَدِكَ، مَاضٍ فِيَّ حُكْمُكَ، عَدْلٌ فِيَّ قَضَاؤُكَ، أَسْأَلُكَ بِكُــــلِّ اسْمٍ هُوَ لَكَ، سَمَّيْتَ بِهِ نَفْسَكَ، أَوْ أَنْزَلْتَهُ فِي كِتَابِكَ، أَوْ عَلَّمْتَهُ أَحَدًا مِنْ خَلْقِكَ، أَوِ اسْتَأْثَرْتَ بِهِ فِي عِلْمِ الْغَيْبِ عِنْدَكَ، أَنْ تَجْعَلَ الْقُرْآنَ رَبِيعَ قَلْبِي، وَنُورَ صَدْرِي، وَجَلَاءَ حُزْنِي، وَذَهَابَ هَمِّي
አላሁመ ኢንኒ አብዱከ፣ ወብኑ አብዲከ፣ ወብኑ አመቲከ፣ ናሲየቲ ቢየዲከ፣ ማዲን ፊየ ሁክሙከ፣ አድሉን ፊየ ቀዷኡከ፣ አስአሉከ ቢኩሊ ኢስሚን ሁወ ለከ፣ ሰመይተ ቢሂ ነፍሰከ፣ አው አንዘልተሁ ፊ ኪታቢከ፣ አው አለምተሁ አሀደን ሚን ኸልቂከ፣ አዊስተእሰርተ ቢሂ ፊ ኢልሚል-ገይቢ ኢንደከ፣ አን ተጅአለል-ቁርአነ ረቢአ ቀልቢ፣ ወ ኑረ ሰድሪ፣ ወ ጀላአ ሁዝኒ፣ ወ ዘሀበ ሀምሚ
አላህ ሆይ! እኔ ባሪያህ፣ የባሪያህ ልጅ እና የሴት ባሪያህ ልጅ ነኝ። ግንባሬ በእጅህ ነው። ፍርድህ በእኔ ላይ ተፈጻሚ ነው፣ ውሳኔህም በእኔ ላይ ፍትሃዊ ነው። ለራስህ በሰየምከው ስም ሁሉ፣ በመጽሐፍህ ባወረድከው፣ ወይም ከፍጥረታትህ ለአንዱ ባስተማርከው፣ ወይም ከአንተ ዘንድ ባለው የሩቅ ሚስጥር እውቀት ውስጥ ለራስህ ብቻ ባስቀረኸው (ስም) ሁሉ እጠይቅሃለሁ፤ ቁርአንን የልቤ የጸደይ ወቅት (ህይወት)፣ የደረቴ ብርሃን፣ የሀዘኔ ማስወገጃ እና የጭንቀቴ መገላገያ እንድታደርግልኝ እጠይቅሃለሁ። አላህ በእርግጥ ጭንቀቶቹን እና ችግሮቹን ያስወግዳል እና በደስታ ይተካቸዋል። ”ተባለ፣ የአላህ መልእክተኛ ሆይ! አንማረውምን? ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ)፣ “በእርግጥ! ይህንን የሰማ ማንኛውም ሰው ሊሀፍዘው ይገባል” አሉ።
Reference: ሰሂህ (አልባኒ) ሲልሲላ ሰሂሃ፡ ፩/፫፻፴፯