Loading...
Language: Amharic
የተበደለ ሰው ዱዓ ተቀባይነት እንዳለው የሚያሳይ ምሳሌ የሰዕድ (ረ.ዐ) ክስተት ከአቡ ሰዕዳህ ጋር ነው። ስለ ሰዕድ (ረ.ዐ) በተጠየቀ ጊዜ፣ ሰዕዳህ እንዲህ አለ፡- «በመሃላ ስላስገደዳችሁኝ፤ ሰዕድ ከሰራዊቱ ጋር ራሱ አይዘምትም ነበር፣ (የጦር ምርኮን) በእኩል አያከፋፍልም ነበር፣ እንዲሁም በህጋዊ ውሳኔዎች ፍትህ አይሰጥም ነበር ብዬ ለመናገር ተገድጃለሁ።» (ይህንን ሲሰሙ) ሰዕድ እንዲህ አሉ፡- «ሶስት ነገሮችን አላህን እለምናለሁ፡- አላህ ሆይ! ይህ ባሪያህ ውሸታም ከሆነ እና ለይውልኝ ከሆነ የቆመው፣ እድሜውን አርዝም፣ ድህነቱን ጨምርበት እና ለፈተና አጋልጠው።» (እንዲሁም ሆነ)። በኋላ ላይ ያ ሰው እንዴት እንደሆነ ሲጠየቅ፡- በሰዕድ እርግማን ምክንያት ፈተና ውስጥ የወደቅኩ ሽማግሌ ነኝ እያለ ይመልስ ነበር። ንዑስ ዘጋቢው አብዱል መሊክ (ረ.ዐ) እንዲህ አለ፡- በኋላ ሳየው በእርጅና ምክንያት ቅንድቦቹ አይኖቹ ላይ ወድቀው ነበር፤ እናም በመንገድ ላይ ትንንሽ ሴት ልጆችን ያስቸግር እና ያጠቃ ነበር።
Reference: ቡኻሪ፡ ፯፻፶፭