Loading...
Language: Amharic
ሰይዱል ኢስቲግፋር (አንድ ጊዜ) -
اَللَّهُمَّ أَنْتَ رَبِّي لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ خَلَقْتَنِي وَأَنَا عَبْدُكَ وَأَنَا عَلَى عَهْدِكَ وَوَعْدِكَ مَا اسْتَطَعْتُ أَعُوْذُ بِكَ مِنْ شَرِّ مَا صَنَعْتُ أَبُوءُ لَكَ بِنِعْمَتِكَ عَلَيَّ وَأَبُوءُ (لَكَ) بِذَنْبِي فَاغْفِرْ لِي فَإِنَّهُ لَا يَغْفِرُ الذُّنُوبَ إِلَّا أَنْتَ
አላሁመ አንተ ረቢ ላ ኢላሀ ኢላ አንተ፣ ኸለቅተኒ፣ ወ አነ አብዱከ፣ ወ አነ አላ አህዲከ ወ ወዕዲከ መሰ-ተጠዕቱ፣ አዑዙ ቢከ ሚን ሸሪ ማ ሰነዕቱ፣ አቡኡ ለከ ቢኒዕመቲከ አለይ፣ ወ አቡኡ (ለከ) ቢዘንቢ ፈግፊርሊ ፈኢነሁ ላ የጉፊሩዝ-ዙኑበ ኢላ አንተ።
አላህ ሆይ፣ አንተ ጌታዬ ነህ፣ ከአንተ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም። ፈጠርከኝ፣ እና እኔ ባሪያህ ነኝ። እኔም በቃልኪዳንህ እና በሩቅ ተስፋህ ላይ በቻልኩት አቅም እገኛለሁ። ከሰራሁት ክፉ ነገር ሁሉ በአንተ እጠበቃለሁ። በኔ ላይ የዋልከውን ጸጋህን አምነን እቀበላለሁ፣ እንዲሁም ኃጢአቴን እቀበላለሁ፤ ስለዚህ ማረኝ፣ ከአንተ በስተቀር ኃጢአትን የሚምር ማንም የለምና። ሸዳድ ቢን አውስ እንደተረኩት ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- «ከአላህ ምህረትን ለመጠየቅ የመጨረሻው (ምርጡ) መንገድ (ከላይ የተጠቀሰው ዱዓ ነው)።» ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) አክለውም እንዲህ አሉ፡- «አንድ ሰው ይህንን በቀን ውስጥ በእርሱ ላይ ጽኑ እምነት ኖሮት ከቀራ እና አመሻሽ (መግሪብ) ከመድረሱ በፊት በዚያው ቀን ከሞተ፣ እርሱ ከገነት ሰዎች ይሆናል። ማንም ሰው ይህንን በማታ በእርሱ ላይ ጽኑ እምነት ኖሮት ከቀራ እና ንጋት ከመድረሱ በፊት ከሞተ፣ እርሱ ከገነት ሰዎች ይሆናል።»
Reference: ቡኻሪ፡ ፷፫፻፮