Loading surah...
Back to Amharic Quran
78 Ayahs • Meccan
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ ٱلرَّحْمَٰنُ
አል-ረሕማን፤
عَلَّمَ ٱلْقُرْءَانَ
ቁርኣንን አስተማረ፡፡
خَلَقَ ٱلْإِنسَٰنَ
ሰውን ፈጠረ፡፡
عَلَّمَهُ ٱلْبَيَانَ
መናገርን አስተማረው፡፡
ٱلشَّمْسُ وَٱلْقَمَرُ بِحُسْبَانٍۢ
ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡
وَٱلنَّجْمُ وَٱلشَّجَرُ يَسْجُدَانِ
ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡
وَٱلسَّمَآءَ رَفَعَهَا وَوَضَعَ ٱلْمِيزَانَ
ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡
أَلَّا تَطْغَوْا۟ فِى ٱلْمِيزَانِ
በሚዛን (ስትመዝኑ) እንዳትበድሉ፡፡
وَأَقِيمُوا۟ ٱلْوَزْنَ بِٱلْقِسْطِ وَلَا تُخْسِرُوا۟ ٱلْمِيزَانَ
መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡
وَٱلْأَرْضَ وَضَعَهَا لِلْأَنَامِ
ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡
فِيهَا فَٰكِهَةٌۭ وَٱلنَّخْلُ ذَاتُ ٱلْأَكْمَامِ
በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡
وَٱلْحَبُّ ذُو ٱلْعَصْفِ وَٱلرَّيْحَانُ
የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡
فَبِأَىِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
خَلَقَ ٱلْإِنسَٰنَ مِن صَلْصَٰلٍۢ كَٱلْفَخَّارِ
ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡
وَخَلَقَ ٱلْجَآنَّ مِن مَّارِجٍۢ مِّن نَّارٍۢ
ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡
فَبِأَىِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
رَبُّ ٱلْمَشْرِقَيْنِ وَرَبُّ ٱلْمَغْرِبَيْنِ
የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡
فَبِأَىِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
مَرَجَ ٱلْبَحْرَيْنِ يَلْتَقِيَانِ
ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡
بَيْنَهُمَا بَرْزَخٌۭ لَّا يَبْغِيَانِ
(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡
Page 1 of 4 (78 ayahs)