Loading surah...
Back to Amharic Quran
96 Ayahs • Meccan
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ إِذَا وَقَعَتِ ٱلْوَاقِعَةُ
መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡
لَيْسَ لِوَقْعَتِهَا كَاذِبَةٌ
ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡
خَافِضَةٌۭ رَّافِعَةٌ
ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡
إِذَا رُجَّتِ ٱلْأَرْضُ رَجًّۭا
ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡
وَبُسَّتِ ٱلْجِبَالُ بَسًّۭا
ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡
فَكَانَتْ هَبَآءًۭ مُّنۢبَثًّۭا
የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ
وَكُنتُمْ أَزْوَٰجًۭا ثَلَٰثَةًۭ
ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡
فَأَصْحَٰبُ ٱلْمَيْمَنَةِ مَآ أَصْحَٰبُ ٱلْمَيْمَنَةِ
የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
وَأَصْحَٰبُ ٱلْمَشْـَٔمَةِ مَآ أَصْحَٰبُ ٱلْمَشْـَٔمَةِ
የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
وَٱلسَّٰبِقُونَ ٱلسَّٰبِقُونَ
(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡
أُو۟لَٰٓئِكَ ٱلْمُقَرَّبُونَ
እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡
فِى جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡
ثُلَّةٌۭ مِّنَ ٱلْأَوَّلِينَ
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
وَقَلِيلٌۭ مِّنَ ٱلْءَاخِرِينَ
ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡
عَلَىٰ سُرُرٍۢ مَّوْضُونَةٍۢ
በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡
مُّتَّكِـِٔينَ عَلَيْهَا مُتَقَٰبِلِينَ
በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡
يَطُوفُ عَلَيْهِمْ وِلْدَٰنٌۭ مُّخَلَّدُونَ
በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡
بِأَكْوَابٍۢ وَأَبَارِيقَ وَكَأْسٍۢ مِّن مَّعِينٍۢ
ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡
لَّا يُصَدَّعُونَ عَنْهَا وَلَا يُنزِفُونَ
ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡
وَفَٰكِهَةٍۢ مِّمَّا يَتَخَيَّرُونَ
ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡
Page 1 of 5 (96 ayahs)