Loading surah...
Back to Amharic Quran
50 Ayahs • Meccan
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ وَٱلْمُرْسَلَٰتِ عُرْفًۭا
ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣
فَٱلْعَٰصِفَٰتِ عَصْفًۭا
በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣
وَٱلنَّٰشِرَٰتِ نَشْرًۭا
መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣
فَٱلْفَٰرِقَٰتِ فَرْقًۭا
መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣
فَٱلْمُلْقِيَٰتِ ذِكْرًا
መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣
عُذْرًا أَوْ نُذْرًا
ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡
إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَوَٰقِعٌۭ
ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡
فَإِذَا ٱلنُّجُومُ طُمِسَتْ
ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡
وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ فُرِجَتْ
ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡
وَإِذَا ٱلْجِبَالُ نُسِفَتْ
ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡
وَإِذَا ٱلرُّسُلُ أُقِّتَتْ
መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡
لِأَىِّ يَوْمٍ أُجِّلَتْ
ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤
لِيَوْمِ ٱلْفَصْلِ
ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا يَوْمُ ٱلْفَصْلِ
የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
أَلَمْ نُهْلِكِ ٱلْأَوَّلِينَ
የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?
ثُمَّ نُتْبِعُهُمُ ٱلْءَاخِرِينَ
ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡
كَذَٰلِكَ نَفْعَلُ بِٱلْمُجْرِمِينَ
በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
أَلَمْ نَخْلُقكُّم مِّن مَّآءٍۢ مَّهِينٍۢ
ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?
Page 1 of 3 (50 ayahs)