Loading surah...
Back to Amharic Quran
40 Ayahs • Meccan
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
عَنِ ٱلنَّبَإِ ٱلْعَظِيمِ
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
ٱلَّذِى هُمْ فِيهِ مُخْتَلِفُونَ
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
كَلَّا سَيَعْلَمُونَ
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
ثُمَّ كَلَّا سَيَعْلَمُونَ
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
أَلَمْ نَجْعَلِ ٱلْأَرْضَ مِهَٰدًۭا
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?
وَٱلْجِبَالَ أَوْتَادًۭا
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
وَخَلَقْنَٰكُمْ أَزْوَٰجًۭا
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
وَجَعَلْنَا نَوْمَكُمْ سُبَاتًۭا
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
وَجَعَلْنَا ٱلَّيْلَ لِبَاسًۭا
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
وَجَعَلْنَا ٱلنَّهَارَ مَعَاشًۭا
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
وَبَنَيْنَا فَوْقَكُمْ سَبْعًۭا شِدَادًۭا
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
وَجَعَلْنَا سِرَاجًۭا وَهَّاجًۭا
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
وَأَنزَلْنَا مِنَ ٱلْمُعْصِرَٰتِ مَآءًۭ ثَجَّاجًۭا
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
لِّنُخْرِجَ بِهِۦ حَبًّۭا وَنَبَاتًۭا
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
وَجَنَّٰتٍ أَلْفَافًا
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
إِنَّ يَوْمَ ٱلْفَصْلِ كَانَ مِيقَٰتًۭا
የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡
يَوْمَ يُنفَخُ فِى ٱلصُّورِ فَتَأْتُونَ أَفْوَاجًۭا
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
وَفُتِحَتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتْ أَبْوَٰبًۭا
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
وَسُيِّرَتِ ٱلْجِبَالُ فَكَانَتْ سَرَابًا
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
Page 1 of 2 (40 ayahs)